Addis Ketema General Secondary School
Announcement የሳይንስና ቴክኖሎጅ የፈጠራ ስራ አውደርዕይ

የሳይንስና ቴክኖሎጅ የፈጠራ ስራ አውደርዕይ

-
|
02:30 AM - 10:00 AM

10ኛው ከተማ አቀፍ የተማሪዎችና የመምህራን የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት በወዳጅነት አደባባይ በድምቀት ተከፈተ።


(ሚያዝያ 16/2017) ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት "በፈጠራ ስራ የተካነ ትጉህ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው አውደ ርዕይ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች በተውጣጡ ተማሪዎችና መምህራን የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች ለህብረተሰቡ ለዕይታ ቀርበዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና የመርሀ ግብሩ የክብር እንግዳ ክብርት ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለይም በከተማችን አዲስ አበባ  የተለያዩ ችግር ፈቺ የሆኑ የፈጠራ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ይህ የፈጠራ ስራ ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲሸጋገር በተማሪዎችና መምህራን የሚሰሩ የፈጠራ ስራዎችን በዚህ መልኩ አውደ ርዕይ በማዘጋጀት ማበረታታት እንደሚገባ በመግለጽ  ከተማ አስተዳደሩም በተማሪዎችና መምህራን የሚሰሩ የፈጠራ ስራዎች ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።


Copyright © All rights reserved.

Created with