Addis Ketema General Secondary School
Announcement የአዲስ ከተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ05/01/2018ዓ.ም ትምህርት አጀማመርን በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል

የአዲስ ከተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ05/01/2018ዓ.ም ትምህርት አጀማመርን በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል

15th September, 2025

የአዲስ ከተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ05/01/2018ዓ.ም ትምህርት  አጀማመርን በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል፤በእለቱ በፕሮግራሙ ላይ የአዲስ ከተማ  ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብሩክ ተክለማሪያም ተገኝተው  አጠቃላይ በ2018ዓ.ም ከትምህርት ማህበረሰቡ የሚጠበቁ ተግባራትን  የገለጹ ሲሆን በዋነኝነት ትምህርት ተቋሙ የተማሪዎችን ውጤትና ስነ-ምግባር ማሻሻል ላይ የበለጠ አጠናክሮ መስራት እንዳለበትና ለዚህም የክፍለ ከተማው ት/ጽ/ቤት  የተጠናከረ ድጋፍ  እንደማይለይ ገልፀዋል፤ የአዲስ ከተማ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ር/መምህር አቶ እንዳልካቸው ደጀኔ በበኩላቸው ከማህበረሰቡ የተረከብናቸውን ልጆች ሁለንተናዊ በሆነ አግባብ በመቅረጽ የሀገር ተረካቢ እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል፤በአጠቃላይ በ2018ዓ.ም ሁለንተናዊ የሆነ የትምህርት ማህበረሰብ የማፍራት ሂደት ላይ  ሁሉም ባለድርሻ አካል እገዛ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው  አንስተዋል፤የትምህርት ቤቱ  ወተመህ ተወካይ ወ/ሮ አጀቡሽ ተዘራ በበኩላቸው ወላጆች ለልጆቻቸው ሁለንተናው  የትምህርት እድገት ላይ  ከት/ቤቱ ጋር በጋራ በመስራት የሚጠበቀውን የተማሪዎች ውጤትና ስነ-ምግባር የማሻሻል ሂደት ላይ  አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል፤በአጠቃላይ የ2018ዓ.ም የትምህርት አጀማመር መርሀ-ግብር እጅግ ባማረ አግባብ ተከውኗል፡፡

.

Copyright © All rights reserved.

Created with